መንግስቱ ለማ "የግጥም ጉባኤ" 1950፥ "ያባቶች ጨዋታ" 1953፥ "ባሻ አሸብር ባሜሪካ 1967" በተሰኙት የሥነ ግጥም ሥራዎቻቸው ለአማርኛ ሥነ ጽሑፍ አዳዲስ የግጥም ስልትና ዘይቤ የመሰረቱ፥ "ያላቻ ጋብቻ" 1956 እና "ጠልፎ በኪሴ" 1961 በተሰኙት ተውኔቶቻቸው ደግሞ "ለኢትዮዽያ ኮሜዲ ቴአትር በር ከፋች" "ኮሜዲያችን ዘመናዊ መልክ እንዲጎናፀፍ ያደረጉ የመጀመሪያው ኢትዮዽያዊ" የሚል ልዩ አክብሮት ያገኙ የሥነ ፅሑፍ ሰው ናቸው።



